ዕድር ኖርዌይ

ዕድር ኖርዌይ

ዕድር ኖርዌይ ዘር፣ ሃይማኖት፣ ጎሳ፣ ቋንቋ፣ የፖለቲካ ድርጅት ሳይለይ ማንኛውም በኖርዊዌይ ውስጥ የሚኖሩ ኢትዮጵያዊያን፣ ኤርትራዊያን እና ሌሎች ፈቃደኛ ዜጎች በአስቸጋሪ የህይወት ክስተቶች ውስጥ በቤተሰብ ወይም በቅርብ ዘመዶች መካከል የሞት አደጋ ሲያጋጥም በገንዘብም ሆነ በማህራዊ ትስስር እርስ በርስ ለመቆምና ለመደጋገፍ እንድንችል ታስቦ በሃገራችን ወግ፣ ባህልና ልማድ መሰረት ታስቦ የተቋቋመ የመረዳጃ ማህበር ነው። ማህበሩ በይፋ ከተቋቋመ ስድስት ወር የሆነው ሲሆን በአሁኑ ወቅት ከመቶ በላይ አባላት አሉት። ስለዚህ ማንኛውም በኖርዊዌይ ውስጥ የምትኖሩ ኢትዮጵያዊያን፣ ኤርትራዊያን እና ሌሎች ፈቃደኛ ዜጎች የዕድሩ አባል በመሆን ተጠቃሚ እንድትሆኑና እንዲሁም ሌላውን እንድትጠቅሙ ጥሪያችንን እያቀርብን ስለማህበሩ ግንዛቤ ለማስጨበጥ ዋና ዋና ነጥቦችን በአጭሩ ለማስቀመጥ እንወዳለን።

Les mer
ዕድር ኖርዌይ አጠቃላይ ስብሰባ አካሄደ

ዕድር ኖርዌይ አጠቃላይ ስብሰባ አካሄደ

ዕድር ኖርዌይ አጠቃላይ ስብሰባውን ሰኞ መጋቢት 28 ቀን 2018 ዓ/ም (06. april 2026) አካሄደ። በዲጂታል(Zoom) በተካሄደው ስብሰባ ላይ በርከት ያሉ በተለያዩ የኖርዌይ ከተሞች የሚገኙ ነባርና አዳዲስ አባላት ተሳትፈዋል። በስብሰባው ላይ የስራ አመራር ኮሚቴው የሥራ እንቅስቃሴና የሂሳብ ሪፖርት ያቀረበ ሲሆን በተሻሻለው ሕገ ደንብ ላይም ሰፊ ማብራሪያ ተስጥቷል። እንዲሁም ከአባላት በተነሱ ጥያቄዎች ላይ ውይይት ተድርጓል። የስራ አመራር ኮሚቴውን በጸሃፊነት የሚያገለግል አንድ አባል እንዲመረጥ ኮሚቴው ባቀረበው ጥያቄ መሰረት ወ/ሮ ብሩክታይት አሉላ ከ Nordland fylke, Bodø ኮሚዩን ዕድሩን በጸሃፊነት ለማገልገል ፈቃደኛነታቸውን ገልጸዋል። በዚሁ መሰረት ለሚቅጥሉት ዓመታት ወ/ሮ ብሩክታይት አሉላ የዕድሩ ጸሃፊ ሆነው ያገለግላሉ። መልካም የአገልግሎት ዘመን እንዲሆንላቸው እንመኛለን።

Les mer
Gnist

Gnist

Gnist የራስ አገልግሎት ፖርታል (Mine sider) ዕድር ኖርዌይ የሂሳብ አያያዝ ፣ የአባልነት ምዝገባ ፣ የድህረ ገጽ ፣ የራስ በራስ አገልግሎት ፖርታል (Gnist) ፣ ወዘተ ጨምሮ በማህበራችን አስተዳደር ውስጥ የ StyreWeb ን ሲስተም ይጠቀማል። ማለትም StyreWeb ለዕድራችን የተሟላ የዘመናዊ ቴክኒኦሎጂ አገልግሎት መፍትሄ አቅራቢያችን ነው ማለት ነው። በዚህ መሰረት የዕድር ኖርዌይ አባላት Gnist APP መጠቀም ይችላሉ። Gnist እንደ የራስ አገልግሎት ፖርታል ወይም Mine sider ተደርጎ መታየት ይችላል። በ Gnist አማካኝነት በዕድር ኖርዌይ ውስጥ ተመዝግበው የሚገኙትን መረጃዎችዎን አጠቃላይ እይታ ማግኘት፣ መለወጥ እና መከታተል ይችላሉ። በGnist አማካኝነት አባላት ከማህበሩ ጋር የቀረበና የተቀናጀ ግንኙነት መፍጠር ይችላሉ። ከማህበሩ የሚመጡ መልዕክቶችንና እንቅስቃሴዎችን አጠቃላይ እይታ ይኖራቸዋል። እንዲሁም የራሳቸውን መረጃ ማዘመን እና ከሌሎች ነገሮች በተጨማሪ የመገለጫ ስዕል (Profilbilde) ማከል ይችላሉ።

Les mer
ዜና ዕረፍት

ዜና ዕረፍት

ወንድማችንና የማህበራችን አባል የሆኑት አቶ መስፍን ሃይሌ ባጋጠማቸው ድንገተኛ የጤና መታወክ ምክንያት በህክምና ሲረዱ ቆይተው ሓሙስ ጥር 28 ቀን 2018 ዓ/ም (05.februar 2026) ከዚህ ዓለም በሞት ተለይተዋል። ቤተሰባቸው፣ ወዳጅ ዘመዶቻቸው፣ ጓደኞቻቸው እንዲሁም በርከት ያሉ ትውልደ ኢትዮጵያውያንና ኤርትራዊያን በተገኙበት ሓሙስ የካቲት 5 ቀን 2018 ዓ/ም (12.februar 2026) ሥርዓተ ቀብራቸው በኦስትረ ግራቭሉንድ (Østregravlund) በክብር ተፈጽሟል። አቶ መስፍን ሃይሌ በሕይወት በነበሩበት ወቅት ትሁት፣ ሰው አክባሪ፣ ስራ ወዳድና በተለይ በቤ/ክ አገልግሎት ከፍተኛ አስተዋጽዖ በማድረግ ላይ የነበሩ ሲሆን ለዕድራችንም ምስረታም የበኩላቸውን አስተውጽዖ አድርገዋል። የዕድራችን የሥራ አመራር ኮሚቴ በማህበሩ አባላት ስም የተሰማውን ጥልቅ ሃዘን እየገለጸ ለቤተሰቦቻቸው መጽናናትን ይመኛል።

Les mer
E-mail: post@eder-norway.com
Mobil: +47 919 08 055
Org.nummer: 932 370 557
Bankkontonr.: 1520.15.06082
Vipps: 961274

ስለዕድሩ ምስረታ ከኖርዌይ በአማርኛ ጋር የተደረገ ቆይታ።

በፌስቡክ ያግኙን